Abstract:
ይህ ጥናት በግእዛ ቋንቋ ከአንድ ጊዚ በላይ የበዙ የግእዛ ቃላትንትን መፈለግና መፈተሽ፦
በሚል ርእስ ተመሥርቶ የተከናወነ ሲኾን፤ አነሣሽ ምክንያቱ በተለምዶ የብዙ ብዙ
እየተባለ የሚታወቁ እና የሚያወግቡ የግእዛ ቃላት በየመጻሕፍቱ ተጽፈው ስለተገኙ ብቻ
ከአንዴድጊዚ በላይ እንደበዙ ተዯርጎ መቆየቱ፤ በአንድ ብዥ ቃል ውስጥ ኹለት አብⶲዎች
መታየታቸው ሲኾን፤ ዐሊማዉም በግእዛ መጻሕፍት እና በምሁራን መጣጥፍች በልማድ
የብኡ ብዙ የሚባለትን እና ኹለት አብⶲ ያሊቸዉን የግእዛ ቃላት መፈለግና መፈተሽ
ነው። ምርምሩ ዐይነታዊ የምርምር ዘዴን የተከተለ ነው። የጥናቱ መረጃ የተሰበስበው
በዋናነት ሰነድ በመፈተሽ ሲኾን፤ ለሙያዉ ቅርብ ለኾኑ ሰዎች ቃለ መጠይቅ በመጠየቅ
እና የቡድን ውይይት በማድረግ ተጨማሪ ሐሳብ ወስዷል። በጥናቱም የግእዛ ነጠላ ቃል
ብዚት የብዙ ብዙ የሚባል በግእዛ ቋንቋ ውስጥ መኖሩን ወይም አለመኖሩን፤ እንዱሁም
አንድ የግእዛ ነጠላ ቃል ከአንድ ጊዚ በላይ መብዛት እንደሌለበት እና መሠረታዊ የብዜት
ሕጉ ምን እንደሚመስል፤ በግእዛ መጻሕፍት ውስጥ የተገለጡበት ኹኔታ፣ የአብⶲዎች
ምንነት ተብራርቷል። እንዱሁም አብⶲነት የልላቸው የግእዛ አብⶲዎች እንዳሉ ጥናቱ
አሳይቷሌ። አጥኚዉ ሰነድ ፍተሻ ሲያደርግ በየቅኔ ቤቱ የሚገኙ የግስ እና የአገባብ
መጻሕፍት ለአንድ ነጠላ ቃል ኹለትና ከዘያ በላይ ብዜት እንዳሉት ተመልክቷል።
የጥናቱ ውጤት ለአንባብያን ግልጥ ይኾን ዘንድ፦ በዘር አወጣጥ ምደባ፤ በቅርጽ ፊደል
ልየታ እንዱሁም የግእዛ ቋንቋ አብⶲዎች የድምፅ አፈጣጠር ኹኔታን በመለየት፤
የአብⶲዎችን ኹኔታ በመገንዘብ የብዙ ብዙ የሚባል ብዜት እንደሌለ እና ለአንድ ብዥ
አንድ ነጠላ፤ ለአንድ ነጠላ አንድ ብዥ እንዳለው ተመላክቷ ል።
በመጨረሻም ይህ ጥናት የብዙ ብዙ የሚባል ብዥ እንደሌለ ለማጥናት ምርምር ሲያደርግ
የአብዥ ፊደላትን ኹኔታ ቢመለከትም፤ ቁጥራቸዉን መወሰን የጥናቱ ከፍል ስላልኾነ
ቁጥራቸዉን ለመወሰን ጥናት ለሚያደርጉ አጥኚዎች እንደመነሻ ኹኖ እንደሚያገለግል እና
ለተጨማሪ ጥናት መነቃቃትን በመፍጠር በኩል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተመላክቷል።