dc.contributor.author | አእምሮ, ይስማው | |
dc.date.accessioned | 2025-07-30T13:40:25Z | |
dc.date.available | 2025-07-30T13:40:25Z | |
dc.date.issued | 2025-07 | |
dc.identifier.uri | http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16817 | |
dc.description.abstract | ይኽ ጥናት የአቡነ ተከሥተ ብርሃን የብራና ቅጅን ይዘት በመተንተን የተሠራ ነው፡፡ ዋና ዓሊማዉም አጠቃሊይ ይዘቱን በመተንተንና ኹሇንተናዊ ፋይዲዉን በማሳየት ተከናውኗል፡፡ይኽ ጥናታዊ ጽሐፍ የጥናት ዳራዉንና መነሻ ሐሳቡን፣ ዓላማዉንና ጥቅሙን እንዲሁም ወሰኑንና ዘዴዉን የሚገልጽ ሲኾን በተጨማሪም ከፅንሰ ሐሳብ አኳያ የገድላት ይዘትንና ጥቅማቸዉ እንዲሁም ከጥናቱ ጋር አንድነትና ልዩነት አላቸው የተባሉ ተዛማጅ ጽሑፎችን ጨምሮ በማካተት ተዳሷል፡፡ እንዲሁም ጥናቱ የገድሉ የጥናት ስነ ዘዴ ምን እንደሚመስል የሚናገር ሲኾን የጻድቁን ገድል የመጀመሪያ ደረጃ የመረጃ ምንጭ በማድረግ እና ሌሎች ኹለተኛ የመረጃ ምንጮችን በመጠቀም በዓይነታዊ የጥናት ዘዴ ትንተናው ተከናውኗል፡፡ የጥናቱን ዋና ማእከል ስለ አቡነ ተከሥተ ብርሃን የሕይወት ታሪክ ልደትና ስያሜ፣ ዕድገትና የትምህርት ኹኔታ፣ ክህነት እና የምንኵስና አገልግሎት፣ አስተዋፅዖና ቃል ኪዳን እንዲኹም ዕረፍተ ሕይወት ተቃኝቶበታል፡፡ በተጨማሪም በገድሉ ውስጥ የተጠቀሱ የስነ ጽሑፍ ጉዳዮች ከእነማስረጃቸው ተተንትነውበታል፡፡ በአጠቃሊይ ጥናቱ ገድሉ ከሃይማኖታዊ ፋይዳቸዉ በተጨማሪ ሊኖራቸው ስለሚችል ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ስነ ምግባራዊ እና ሌሎችም ጥቅሞች እንዳሉትም የቀረበበት ሲኾን በመጨረሻም ደግሞ የጥናቱ ማደማደመሚያ እና ለተጨማሪ ተግባራት ምክረ ሐሳብ የተጠቆመበት ኾኖ ምርምሩ ፍጻዉን አግኝቷል | en_US |
dc.language.iso | en | en_US |
dc.subject | Geʽez | en_US |
dc.title | የይዘት ትንተና በአቡነ ተከሥተ ብርሃን ገድል | en_US |
dc.type | Thesis | en_US |