BDU IR

የተማሪዎች አንብቦ የመረዳት ብልሀት አጠቃቀም ከአንብቦ መረዳት ውጤታቸው ጋር ያለው ተዛምዶ፣ በዱከም ከተማ በሚገኘው ኦዳ ነቤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተተኳሪነት

Show simple item record

dc.contributor.author ታደለ, አልማዝ
dc.date.accessioned 2019-10-15T05:38:21Z
dc.date.available 2019-10-15T05:38:21Z
dc.date.issued 2019-10-15
dc.identifier.uri http://hdl.handle.net/123456789/9894
dc.description.abstract አህጽሮተ ጥናት የጥናቱ ዋና አላማ የ 9ኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት አንብቦ የመረዳት ብልሀት አጠቃቀም ከአንብቦ መረዳት ውጤታቸው ጋር ያለውን ተዛምዶ መመርመር ነው፡፡የጥናቱ ተተኳሪዎች በዱከም ከተማ አስተዳደር በሚገኝ ኦዳነቤ ትምህርትቤት በ 2011 ዓ.ም የሚማሩ የ 9ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ የዱከም ኦዳነቤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ብዛት ሴት= 530 ወ=380 በድምሩ 910 ናቸው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ካሉት 14 ክፍሎች (ሴክሽኖች) አራቱን ክፍሎች በሎተሪ የናሙና አመራረጥ በመምረጥ ከየክፍሎቹ 20 ተማሪዎችን በብድግ ብድግ ናሙና ለጥናቱ ተተኳሪ የሆኑ 30 ወንድና 50 ሴት በድምሩ 80 ተማሪዎች በእድል ሰጭ የንሞና ዘዴ ተመርጠዋል፡፡ ከእነሱም አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች በጽሁፍ መጠይቅና በፈተና ተሰብስበዋል፡፡ የጽሁፍ መጠይቁ የተማሪዎቹን አንብቦ የመረዳት ብልሃት አጠቃቀም ለመመርመር በሚያስችል መልኩ ከተከናወነ በኋላ መረጃዉ ተሰብስቧል፡፡ፈተናው ደግሞ አንብቦ የመረዳት ውጤታቸው ምን እንደሚመስል ለመመርመር ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ በሁለቱ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች የተገኙት መረጃዎች በመጠናዊና በአይነታዊ ተተንትነዋል፡፡ የተማሪዎች አንብቦ የመረዳት ብልሃት አጠቃቀምና አንብቦ የመረዳት ውጤት ምን እንደሚመስል ተመርምሮ የተገኘው ውጤት በነጠላ ናሙና ቲ-ቴስት፣ በአንብቦ የመረዳት ብልሃት አጠቃቀምና በአንብቦ መረዳት ውጤት መካከል ተዛምዶ መኖሩን በፒርሰን ተዛምዶ ሥሌት ቀመር፣አንብቦ የመረዳት ብልሃት አንብቦ የመረዳት ውጤትን ለመተንበይ ያስችል እንደሆነ ለመመርመር በቀላል ድህረት ትንተና ስታስቲካዊ ዘዴዎች ተተንትነዉ ተብራርተዋል፡፡ በትንተናው መሰረት በአንብቦ መረዳት ብልሀትና በአንብቦ መረዳት ውጤት መካከል ጉልህ ተዛምዶ (r=.380 ,P̄= .001 ) ታይቷል፡፡ ይህም አንብቦ የመረዳት ብልሀት ሲጨምር በአንብቦ የመረዳት ውጤት ላይ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው አመላክቷል፡፡ በጥናቱ አንብቦ የመረዳት ብልሀት የአንብቦ መረዳት ውጤትን ለመተንበይ ያስችል እንደሆነ ተመርምሮ በአዎንታዊ የሚተነብይ ሆኖ ተገኝቷል (B = .380, t= 5.486, P= .000)፡፡ በመሆኑም የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ብልሀት አጠቃቀም ከአንብቦ መረዳት ውጤት ጋር በማዛመድ መጠቀም ጠቃሚ መሆኑን አጥኝዋ ትጠቁማለች፡፡ en_US
dc.language.iso en_US en_US
dc.subject አማርኛ en_US
dc.title የተማሪዎች አንብቦ የመረዳት ብልሀት አጠቃቀም ከአንብቦ መረዳት ውጤታቸው ጋር ያለው ተዛምዶ፣ በዱከም ከተማ በሚገኘው ኦዳ ነቤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተተኳሪነት en_US
dc.type Thesis en_US


Files in this item

This item appears in the following Collection(s)

Show simple item record