dc.contributor.author | ጥንቅሽ, ደሴ | |
dc.date.accessioned | 2022-11-17T12:30:05Z | |
dc.date.available | 2022-11-17T12:30:05Z | |
dc.date.issued | 2022-11 | |
dc.identifier.uri | http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/14454 | |
dc.description.abstract | የዚህ ጥናት ዋና አላማ የተማሪዎች ግለብቃት እምነት ከመጻፍ ችሎታ ጋር ያለውን ተዛምዶ መመርመር ነበር፡፡ ጥናቱ ተዛምዷዊ ንድፍን የተከተለ ሲሆን ገላጭ የምርምር ስልትን ተከትሎ የቀረበ ነው፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች ለመምረጥ ቀላል የእጣ ናሙናን በመጠቀም ተመርጠዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ በሙጃ ሮቢት አጠቃላይ ከፍተኛ መሰናዶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2014 ዓመተ ምህረት በዘጠነኛ ክፍል የሚማሩ 117 ተማሪዎች ናቸው፡፡ መረጃዎቹ በጽሁፍ መጠይቅ እና በመጻፍ ችሎታ መለኪያ ፈተና ተሰብስበዋል፡፡ መረጃዎቹም መጠናዊ የምርምር ዘዴን በመጠቀም በ(SPSS 23)ኮምፒውተር ሶፍት ዌር በፒርሰን ተዛምዶ ተሰልቶ ትንተና ተተንትነዋል፡፡ በጽሁፍ መጠይቅ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት የተማሪዎች ግለብቃት እምነት በጥቅል የመጻፍ ችሎታን የመተንበይ ድርሻው R²(0.964) ወይም (96.4%) ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በተማሪዎች ግለብቃት እምነት የመጻፍ ችሎታ መካከል ያለው ተዛምዶ በተመለከተ 0.981 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በመሆኑም በተማሪዎች ግለብቃት እምነት እና በመጻፍ ችሎታ መካከል አወንታዊና ጉልህ የሆነ ተዛምዶ እንዳለው በስታትስቲክስ ጉልህ ልዩነት ታይቷል፡፡ በመሆኑም የስርዓተ ትምህርት አዘጋጆች የቋንቋ መማሪያና መስተማሪያ ሲዘጋጁ የተማሪዎችን የመጻፍ ችሎታ ሊያዳብሩ የሚችሉ የግለብቃት እምነት ስልጠናዎች እንዳንድ ይዘት አካተው ቢያቀርቡ፣ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የሚያስተምሩትን የመጻፍ ችሎታ ትምህርት ሲያቅዱ፣ ሲተገብሩና ሲገመግሙ የተማሪዎችን ግለብቃት እምነት ግምት ውስጥ ያስገባ ቢሆንና የሚሰጧቸው ተግባራትና መልመጃዎች የግለብቃት እምነት ገፅታዎችን መጠቀም የሚያስችሉ ቢደረግ እና በቀጣይ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ለማጥናት ፍላጎት ያላቸው አጥኝዎች በስፋት በመመልከት ከሌሎች ተለዋዋጮች ጋር በማቀናጀት ቢሰሩ ለመጻፍ ችሎታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሊገኝ ይችላል የሚሉ የመፍትሄ ሀሳቦች ተጠቁመዋል፡፡ | en_US |
dc.language.iso | en_US | en_US |
dc.subject | Ethiopian Languages and Literature - Amharic | en_US |
dc.title | የተማሪዎች ግለብቃት እምነት (Self-efficacy) ከመጻፍ ችሎታቸው ጋር ያለው ተዛምዶ ፤በ9ኛ ክፍል ተተኳሪነት የትምህርት ማስተርስ ዲግሪ ከፊል ማሟያ የቀረበ ጥናት | en_US |
dc.type | Thesis | en_US |