BDU IR

የማንበብ ግል ብቃት እምነት ከተማሪዎች የአንብቦ መረዳት ችሎታ ጋር ያለው ተዛምዶ፦በ10ኛ ክፍል ተተኳሪነት

Show simple item record

dc.contributor.author ካሳ, አባይ
dc.date.accessioned 2020-02-04T12:54:11Z
dc.date.available 2020-02-04T12:54:11Z
dc.date.issued 2020-02-04
dc.identifier.uri http://hdl.handle.net/123456789/10112
dc.description.abstract የዚህ ጥናት ዋና አላማ የማንበብ ግለብቃት እምነት ከአንብቦ መረዳት ችሎታ ጋር ያለውን ተዛምዶ መፈተሽ ነው፡፡በዚህ ጥናት የተሳተፉትም በጉጂ ዞን በዋደራ ወረዳ ሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤት በ2011 ዓ.ም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ 342 ተማሪዎች በተራ የናሙና ዕጣ ዘዴ መሰረት የተመረጡ 80 የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ጥናቱ የተከተለው የአጠናን ዘዴም ተዘምዷዊ ነው፡፡በመሆኑም የተማሪዎችን የማንበብ ግለብቃት ለመለካት በፅሁፍ መጠይቅ፤የአንብቦ መረዳት ችሎታቸውን ለመፈተሸ ደግሞ በአንብቦ መረዳት ፈተና መረጃ ተሰብስቧል፡፡የተሰበሰበው መረጃም በፒርሰን የተዛምዶ ስሌት ቀመር መሰረት ተተንትኗል፡፡በግኝቱ መሰረትም በሁለቱ ተላውጦዎች (በማንበብ ግለብቃት እምነትና በአንብቦ መረዳት ችሎታ) መካከል አወንታዊ ተዛምዶ ተገኝቷል፡፡የተዛምዶው መጠንም 0.085 ሆኗል፡፡ሆኖም ግን የተዛምዶው መጠን ሲታይ ዝቅተኛ በመሆኑ የጉልህነት መጠኑ በ0.05 የስህተት ይሁንታ መጠን(sig)፣በ80 የነፃነት ደረጃ(df)፣ በባለሁለት ጫፍ ፍተሻ(2-tailed) ተፈትሾ የተዛምዶ መጠኑ ጉልህ ያልሆነ ዝቅተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለ ተመልክቷል፡፡ሌላው የማንበብ ግለብቃት እምነታቸው አማካይ ውጤትም በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ እንዲሁም የአንብቦ መረዳት ችሎታቸው አማካይ ውጤትም በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ በተጨማሪም የማንበብ ግለብቃት እምነት ከተማሪዎች ከተገኘው የአንብቦ መረዳት ውጤት ውስጥ 0.7%(R 2 = 0.007) ያህል ድርሻ ብቻ እንደለው ተመልክቷል፡፡በጥናቱ በተገኘው ውጤት መሰረት የተማሪዎች የማንበብ ግለብቃት እምነት የሚያሳድጉ ስልቶችን በመጠቀም የተማሪዎችን የአንብቦ መረዳት ችሎታን ማሳደግ ያስፈልጋል የሚል የመፍትሄ ሀሳብ ቀርቧል en_US
dc.language.iso en_US en_US
dc.subject አማርኛ en_US
dc.title የማንበብ ግል ብቃት እምነት ከተማሪዎች የአንብቦ መረዳት ችሎታ ጋር ያለው ተዛምዶ፦በ10ኛ ክፍል ተተኳሪነት en_US
dc.type Thesis en_US


Files in this item

This item appears in the following Collection(s)

Show simple item record