<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<rss xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/" version="2.0">
<channel>
<title>Geʽez</title>
<link>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/11084</link>
<description/>
<pubDate>Mon, 13 Jul 2026 14:41:29 GMT</pubDate>
<dc:date>2026-07-13T14:41:29Z</dc:date>
<item>
<title>ፍጹም አማርኛ የመስሉትን ጥቂት የግእዝ ቃላትን ማስተዋወቅ</title>
<link>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16872</link>
<description>ፍጹም አማርኛ የመስሉትን ጥቂት የግእዝ ቃላትን ማስተዋወቅ
ተዋበ, ሞስዬ
ይህ ጥናት ፍጹም አማርኛ የመስሉትን ጥቂት የግእዝ ቃላትን መተንተን እና ማስተዋወቅ&#13;
በሚል ርእስ ተመሥርቶ የተከናወነ ሲሆን አነሣሽ ምክንያቱ በተለምዶ የግእዝ ቃላትን&#13;
የአማርኛ ቃላት አስመስሎ የመረዳት ባኅሪ በማኅበረሰቡ ዘንድ ይስተዋላል፡፡እንዲሁም የግእዝ&#13;
ቋንቋ በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ መነገሩ እየተዳከመ ከመምጣቱ ጋር ተየይዞ ጨርሶ&#13;
እንደሞተ ቋንቋ ተደርጎ በመወሰዱ ነው ፡፡ ዐላማውም በግእዝ፣በአማረኛ መጻሕፍት እና&#13;
በምሁራን መጣጥፎች እነዚህ ፍጹም አማርኛ የመሰሉ የግእዝ ቃላትን መፈለግ፤መኖራቸውን&#13;
እና አለመኖራቸውን ማረጋገጥ ነው፡፡ ምርምሩ አይነታዊ የምርምር ዘዴን የተከተለ ነው፡፡&#13;
የጥናቱ መረጃ የተሰበሰበው በዋናነት ሰነድ በመፈተሽ ሲኾን ለሙያው ቅርብ የኾኑ ሰዎችን&#13;
ቃለ መጠይቅ በመጠየቅ ተጨማሪ ሐሳብ ወስዷል፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ ፍጹም አማርኛ&#13;
የመሰሉ የግእዝ ቃላት መኖር እና አለመኖራቸውን በመሠረታዊነት ማረጋገጥ እንዲቻል ነው፡፡&#13;
እንደዚሁም እነዚህ የሚፈለጉ ቃላት በተጨባጭ እንዳሉ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ አጥኝዉ ሰነድ&#13;
ፍተሻ ሲያደርግ በየቅኔ ቤቱ የሚገኙ የግስና የአገባብ መጻሕፍትን ፍጹም አማርኛ የመሰሉ&#13;
የግእዝ ቃላት እንዳሉት ተመልክቷል፡፡ የጥናቱ ውጤት ላንባቢያን ግልጥ ይሆን ዘንድ በዘር&#13;
አወጣጥ ምደባ እና በቅርፀ ፊደል ልየታ እንዲሁም የግእዝ ቋንቋ ቃላትን በመለየት ፍጹም&#13;
አማረኛ የመሰሉትን የግእዝ ቃላት እንዳሉ ተመላክቷል፡፡ በመጨረሻም ይህ ጥናት ፍጹም&#13;
አማረኛ የመሰሉ የግእዝ ቃላት በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች የተገኙ እንደሆነ&#13;
እና ጥናት እና ምርምር ለማድረግ ለሚፈልግ ተመራማሪ ቁጥራቸው ያልተገደበ በመኾኑ&#13;
ለዠደፊት ለተጨማሪ ጥናት መነቃቃትን በመፍጠር በኩል አስተዋፅኦ እንደሚኖረው&#13;
ተመላክቷል፡፡
</description>
<pubDate>Sun, 01 Jan 2017 00:00:00 GMT</pubDate>
<guid isPermaLink="false">http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16872</guid>
<dc:date>2017-01-01T00:00:00Z</dc:date>
</item>
<item>
<title>Analyzing Traditional Remedies for Chronic Cough Treatment in Ge ez Manuscripts</title>
<link>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16864</link>
<description>Analyzing Traditional Remedies for Chronic Cough Treatment in Ge ez Manuscripts
Simeneh, Haymanot
This study examines traditional remedies for chronic cough preserved in three ancient Gəʽəz medicinal manuscripts: ʾƎšädäbdäbbe (IES 713), Mäṣḥafä Mädḥanit (IES 2444), and Mäṣḥafä Fäws (ETHIOPIEN 402 GURIAULE 98), to document, analyze, and interpreting indigenous therapeutic knowledge to contribute to the preservation and scholarly understanding of Ethiopian traditional medicine. A qualitative research approach was employed, using a descriptive and analytical design to systematically document remedies and interpret their cultural significance. Purposive sampling was applied to deliberately select key informants, including traditional healers, scholars, modern physicians, and patients, who provided in-depth perspectives. The primary data were obtained from detailed analyses of the three medicinal manuscripts and from semi-structured interviews with selected informants, whereas the secondary data were drawn from books, journal articles, and related literature that offered historical and cultural perspectives. Data were analyzed thematically following Braun and Clarke’s framework. Braun and Clarke’s thematic analysis is a qualitative approach that involves identifying implicit or explicit ideas within the data. The findings revealed over twenty medicinal herbs, nine medicinal foods, five functional foods, as well as minerals and animal-derived substances such as bile and urine employed in treatment protocols, with dosage, frequency, and modes of administration guided by prescriptive rules (Gäbir). Significant regional variations in plant nomenclature, remedy preparation, and ceremonial practices were observed, reflecting both cultural richness and the lack of standardization, while diagnostic techniques, therapeutic procedures, and indigenous naming systems further illuminated the depth of Ethiopian traditional medical knowledge. The study concludes that these manuscripts and practices embody not only therapeutic knowledge but also cultural values and worldviews, and by preserving this heritage, it provides a solid foundation for future ethnobotanical and pharmacological research while contributing to the safeguarding of Ethiopia’s intangible cultural heritage.
</description>
<pubDate>Fri, 01 Aug 2025 00:00:00 GMT</pubDate>
<guid isPermaLink="false">http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16864</guid>
<dc:date>2025-08-01T00:00:00Z</dc:date>
</item>
<item>
<title>የይዘት ትንተና በገድለ አቡነ አናንያ</title>
<link>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16849</link>
<description>የይዘት ትንተና በገድለ አቡነ አናንያ
ያሬድ, ደስታው
ይህ ጥናት በገድለ አቡነ አናንያ የይዘት ትንተና ላይ በሚል ርእስ የተነሣዉ፡ በጥናቱ ዳራ&#13;
የተለያዩ ምሁራን ስለ ኢትዮጵያ ፊደልና ሥነ ጽሑፍ ሀብት የሰጡትን አስተያየት&#13;
ለማስተዋወቅ ሞክሯል። የጥናቱን አነሣሽ ምክንያት የጠቆመ ሲኾን ጥናቱ በምርምር&#13;
ሥራዉ፣ ዐላማዉን በግልጽ አስቀምጧል። ጥናቱ ከተካሄደ በኋላ ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበት&#13;
ኹሉም የሚያምንበት እንደመኾኑ መጠን ይህ ጥናትም መጠነ ሰፊ የኾነ ጠቀሜታ&#13;
እንደሚሰጥ በዝርዝር ተቀምጧል። ምርምሩ ዐይነታዊ የምርምር ዘዴን የተከተለ ነው።&#13;
በተጨማሪም የጥናቱ መሠረታዊ የአጠናን ዘዴ ኹለንተናዊ አካላት የኾኑት የመረጃ&#13;
ምንጮች፣ የናሙና አመራረጥ ዘዴ፣ የመረጃ ማሰባሰቢያ መሣሪያዎች እና የመረጃ መተንተኛ&#13;
ዘዴ የሚሉት በየቅደም ተከተል ደረጃቸዉ ተብራርተዋል። በአጠቃላይ አጥኚዉ መሪ&#13;
ጥያቄዎቹን ለመመለስ ባደረገዉ ጥረት ከተለያዩ የጥናት ውጤቶችና መዛግብት የተገኙ&#13;
መረጃዎችን በመፈተሽ ምርምር በማድረግ የገድሉን ይዘት በመተንተን መልእክቱን&#13;
በማብራራት አቅርቧል።
</description>
<pubDate>Sat, 01 Jun 2024 00:00:00 GMT</pubDate>
<guid isPermaLink="false">http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16849</guid>
<dc:date>2024-06-01T00:00:00Z</dc:date>
</item>
<item>
<title>የይዘት ትንተና በገድለ አብርሀ ወአጽብሐ</title>
<link>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16830</link>
<description>የይዘት ትንተና በገድለ አብርሀ ወአጽብሐ
ፈንታሁን, ደሴ
ይህ ጥናት የገድለ አብርሀ ወአጽብሐ የይዘት ትንተና በሚል ርእስ ላይ የተሠራ ሲኾን&#13;
ጥናቱን ለመሥራት አነሣሽ ምክንያቶችም ተመላክተዋል፡፡ ቅዱሳን ነገሥት አብርሀ&#13;
ወአጽብሐ በስማቸው ትምህርት ቤት የተሠራላቸው፣ በቤተክርስቲያን በዓል&#13;
የሚከበርላቸው ምን ቢሠሩ ነው ? የሚል ጥያቄ አጥኚዉ ስለነበረው&#13;
ገድሉን&#13;
ለማጥናት እንደ አነሳሳው ተገልጧል&#13;
፡፡ ዐቢይ ዐላማውም ገድለ አብርሀ ወአጽብሐን&#13;
በመተንተን&#13;
አብርሀ ወአጽብሐ እነማን ነበሩ፣&#13;
ያላቸውን ታሪካዊ፣ ስነ ጽሑፋዊ፣&#13;
ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ሃይማኖታዊ ፋይዳ ማሳየት ሲኾን ዐይነታዊ የምርምር&#13;
ዘዴን ተከትሎ መረጃዎችን በገላጭ የትንተና ሥልት በመተንተን ተከውኗል&#13;
፡፡&#13;
ይህንንም ዐላማ ለማሳካት በዋናነት አንድ የብራናዉን ገድል ቅጅ ቀዳማይ የመረጃ&#13;
ምንጭ በማድረግ የተጠቀመ ሲኾን፤ ሌሎች ከገድለ አብርሀ ወአጽብሐ ጋር ዝምድና&#13;
ያላቸው ወይም ስለ ገድሉ ተጨማሪ መረጃ የሰጡ መጻሕፍት፤ መጽሔቶች፣ ጥናታዊ&#13;
ጽሑፎች እንደ ኹለተኛየመረጃ ምንጭ ተጠቅሟል፡፡ ይህም ጥናት በዓይነታዊ የጥናት&#13;
ዘዴ ተተንትኖ ቀርቧል፡፡&#13;
ጥናቱ የገድልን ምንነት ከፅንሰ ሐሳብ አንጻር ያብራራ&#13;
ሲኾን በግእዝ ስለተጻፉ ገድላት ታሪካዊ ዳራ ማብራሪያ ሰጥቷል&#13;
፡፡&#13;
በገድሉ ስነ&#13;
ጽሑፋዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ሃይማኖታዊ ፋይዳ ላይ ሰፊ ትንተና&#13;
ያደረገ ሲኾን በመጨረሻም ሌሎች ቅጆችን በማሰባሰብ በገድሉ ላይ የተመሳከረ&#13;
አርትዖት እና የትርጒም ሥራ ቢሠራበት፣ ተመራማሪዎች ይህን ጥናት እንደመነሻ&#13;
ተጠቅመው ክፍተቱን ቢሞሉ መልካም ይኾናል የሚሉ የይኹንታ ሐሳቦችን&#13;
አስቀምጧል፡
</description>
<pubDate>Wed, 01 Feb 2017 00:00:00 GMT</pubDate>
<guid isPermaLink="false">http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/16830</guid>
<dc:date>2017-02-01T00:00:00Z</dc:date>
</item>
</channel>
</rss>
