<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/" xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom">
<title>Thesis and Dissertations</title>
<link href="http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/1941" rel="alternate"/>
<subtitle/>
<id>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/1941</id>
<updated>2001-01-13T06:37:24Z</updated>
<dc:date>2001-01-13T06:37:24Z</dc:date>
<entry>
<title>በጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ማኅበረሰብ ለቤት እንስሳት ደኅንነት የሚደረግ  ሥርዓተ ከበራ በሐምሌ ኪሮስ ማሳያነት</title>
<link href="http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15819" rel="alternate"/>
<author>
<name>በማተቤ, ጥላሁን</name>
</author>
<id>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15819</id>
<updated>2024-05-29T13:06:14Z</updated>
<published>2015-06-01T00:00:00Z</published>
<summary type="text">በጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ማኅበረሰብ ለቤት እንስሳት ደኅንነት የሚደረግ  ሥርዓተ ከበራ በሐምሌ ኪሮስ ማሳያነት
በማተቤ, ጥላሁን
ይህ ጥናት “በጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ማኅበረሰብ ለቤት እንስሳት ደኅንነት የሚደረግ ሥርዓተ&#13;
ከበራ በሐምሌ ኪሮስ ማሳያነት” በሚል ርእስ የሐምሌ ኪሮስ ሥርዓተ ከበራ ክዋኔን&#13;
በመመርመር ማህበረሰቡ ስርዓተ ከበራውን ለቤት እንስሳት ደኅንነት ማስጠበቂያነት&#13;
የሚገለገሉበትን እውቀትና ሥርዓት ማሳየት የሚል ዐቢይ ዓላማ ያለው ሲሆን የኪሮስ ስርዓተ&#13;
ከበራ ሐምሌ ስምንት ቀን የሚከበርበትን ምክንያት መግለጽ፤ ለቤት እንስሳት ደህንነት&#13;
የሚደረገውን የሐምሌ ኪሮስ ሥርዓተ ከበራ ክዋኔ ሂደት ማሳየት፤ በስርዓተ ከበራ ላይ ያሉ&#13;
ተምሳሌቶችን መተርጎም፤ ተተኳሪው ማህበረሰቡ ስለ ቤት እንሳሳት ደህንነት ያለውን&#13;
አመለካከትና እውቀት ማብራራት የሚሉ ንዑስ ዓላማዎች የያዘ ነው፡፡ መረጃዎች በምልከታ፣&#13;
በቃለ መጠይቅና በተተኳሪ የቡድን ውይይት ዘዴዎች በመጠቀም እና 20 ወንዶችን፣ 5 &#13;
እንስሳት የሚያግዱ (የሚጠብቁ ልጆች /እረኞች) እና 10 ሴቶች በአጠቃላይ 35 የመረጃ&#13;
ሰጪዎች ተሳታፊ በማድረግ ተሰብስበዋል፡፡ መረጃ ሰጪዎች በዓላማ ተኮር እና በጠቋሚ&#13;
ናሙና ዘዴ በመጠቀም ተመርጠዋል፤ የተሰበሰቡት መረጃዎች በክዋኔያዊ፣ ማህበራዊ ግንባታ፣&#13;
በእንስሳት ደኅንነት ማሕቀፍ እና ስነ ፍች ንድፈ ሃሳቦች ተተንትነው ቀርበዋል፡፡ በትንታኔው&#13;
መሰረት የሐምሌ ኪሮስ ስርዓተ ከበራ ለቤት እንስሳት ደኅንነት ተብሎ ሐምሌ ስምንት አባ&#13;
ኪሮስ ያረፈበትን በማሰብና እግዚአብሔር የገባለትን ቃል ኪዳን መነሻ በማድረግ ማህበረሰቡ&#13;
የራሱን ሀገር በቀል እውቀትና እሴት በመጨመር የሚከውነው፤ ሃይማኖታዊ በዓል ነው፤&#13;
ለስርዓተ ከበራው ክዋኔ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በማዘጋጀት ሐምሌ ስምንት ቀን የተመረጠና&#13;
ሁሉም አባላት የተስማሙበት ተባእት በግ በማረድ እንስሳት ደም የሚረጩበት የከብቶች ቀን&#13;
በዓል እንደሆነ ጥናቱ ይጠቁማል፡፡ ስርዓተ ከበራው የራሱ የሆኑ የክዋኔ ሂደቶች እንዳሉት&#13;
ጥናቱ አሳይቷል፡፡ የሚጠቡ እንቦሶች (ጥጃዎች) በነፃነት ከእናታቸው ጋር የሚውሉበት ቀን&#13;
እንደሆነ፤ በስርዓተ ከበራው ክዋኔ ዕለት የሚቀርቡ ቁሳዊ ባህሎች በአብዛኛው የእንስሳት&#13;
ተዋጽኦዎች እንደሆኑ የመስክ መረጃዎች ጠቁመዋል፤ ማህበረሰብ ስለ ቤት እንስሳት ደህንነት&#13;
የሚከውናቸው በርካታ ልማዶች እንዳሉት ጥናቱ አስረድቷል፡፡ የማህበረሰቡ የቤት እንስሳትን&#13;
ደህንነት ለመጠበቅና ለማስጠበቅ የሐምሌ ኪሮስ ስርዓተ ከበራ በመፈጸም ስርዓተ ከበራ ለጤና&#13;
ፈውስ የሚሰጥ መሆኑን ተጠኚው ማህበረሰብ ይጠቁማል፡፡ ይህ መረጃ የጥናቱ ትንተና ክፍል&#13;
ላይ ተጠቁሟል፡፡ በዚህም መሰረት ስርዓተ ከበራ የጤና ፈውስ መሆኑን ጥናቱ አመላክቷል፡፡&#13;
የሐምሌ ኪሮስ ስርዓተ ከበራ በማህበረሰቡ አባላት ውስጥ አንዳንድ ሰዎች በአባ ኪሮስ&#13;
ወርሃዊና ዓመታዊ ስርዓተ ከበራ ጊዜ በቤት እንስሳት ላይ የተለያዩ በሽታዎችና አደጋዎች&#13;
መከሰታቸው እና በአባ ኪሮስ ስም ፀበልና ረፍታቸውን መሰረት በማድረግ በሚፈጽሙት&#13;
ስርዓተ ከበራ አማካኝነት እንስሳት እንደሚፈወሱ እና በአንዳንድ ሰዎች የደረሰው ችግርና&#13;
በረከት እንዲደርሳቸውና እንስሳቶች ታመው እንደዳኑላቸው ተጠኚዎች ያብራራሉ፡፡ በመኖር&#13;
ሂደት ሌሎች ችግሮች እንዳይገጥሟቸው አስቀድመው ለመከላከል እና የተከሰቱ ችግሮችንም&#13;
ለማስወገድ ሲባል የሚከውኑት ስርዓተ ከበራ እንደሆነ በጥናቱ ተመላክቷል፡፡ &#13;
ቁልፍ ቃላት፡- ሐምሌ ኪሮስ ከበራ፣ የቤት እንስሳት፣ ደህንነት፤ ሃይማኖትና እምነት
</summary>
<dc:date>2015-06-01T00:00:00Z</dc:date>
</entry>
<entry>
<title>የጅራፍ ግርፍርፊያ ጨዋታ ክዋኔ ትንተና በቡሄ በዓል ማሳያነት በላይ ጋይንት ወረዳ ማኅበረሰብ</title>
<link href="http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15818" rel="alternate"/>
<author>
<name>በተስፋዬ, አበባው</name>
</author>
<id>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15818</id>
<updated>2024-05-29T12:13:14Z</updated>
<published>2015-01-01T00:00:00Z</published>
<summary type="text">የጅራፍ ግርፍርፊያ ጨዋታ ክዋኔ ትንተና በቡሄ በዓል ማሳያነት በላይ ጋይንት ወረዳ ማኅበረሰብ
በተስፋዬ, አበባው
ይህ ጥናት "የጅራፍ ግርፍርፊያ ጨዋታ ክዋኔ በቡሄ በዓል ማሳያነት" ምን እንደሚመስል&#13;
በመመርመር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ በቡሄ በዓል ጅራፍ ግርፍርፊያ ጨዋታ የሚገጠሙ&#13;
ቃል ግጥሞችን ይዘት መተንተን፣ የቡሄ በዓል ጅራፍ ግርፍርፊያ ጨዋታ ፋይዳ ማሳየት&#13;
የሚሉ ናቸው። ከቀዳማይ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ውስጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምልከታና&#13;
የቡድን ውይይትን በመጠቀም ከመስክ መረጃ ተሰብቧል፡፡ ከመስክ የተገኙትን መረጃዎች&#13;
በመልክ በመልክ በማደራጀት አይነታዊ የምርምር ዘዴን በመጠቀም በተግባራዊ፣ መዋቅራዊና&#13;
ክዋኔያዊ ንድፈ ሃሳቦች በመታገዝ በገለፃ መልክ ተተንትኖ ቀርቧል፡፡ በጥናቱ ላይ የላይጋይንት&#13;
ወረዳ ማህበረሰብ የጅራፍ ግርፍርፊያ ጨዋታ ለማህበረሰቡ አካላዊ፣ ስነልቡናዊ እና&#13;
ሃይማኖታዊ ፋይደ እንዳለው ያስረዳል፡፡ ይህ ባህላዊ ጨዋታ የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል&#13;
የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት፣ የወረዳው ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ሌሎች ማህበረ ባህላዊ ተቋማት&#13;
ትኩረት ቢያደርጉበት መልካም ነው።
</summary>
<dc:date>2015-01-01T00:00:00Z</dc:date>
</entry>
<entry>
<title>አጎላጎሌ ጨዋታ ክዋኔና ፋይዳ በጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ማህበረሰብ</title>
<link href="http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15776" rel="alternate"/>
<author>
<name>አየሁ, ንጉሴ</name>
</author>
<id>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15776</id>
<updated>2024-05-08T12:18:33Z</updated>
<published>2016-07-01T00:00:00Z</published>
<summary type="text">አጎላጎሌ ጨዋታ ክዋኔና ፋይዳ በጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ማህበረሰብ
አየሁ, ንጉሴ
ይህ ጥናት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የአጎላጎሌ ጨዋታ&#13;
ክዋኔና ፋይዳ በጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ማህበረሰብ በሚል ርዕስ ትኩረት ተደርጓል፡፡ የጥናት&#13;
ዋና ዓላማ የአጎላጎሌ የልጆች ጨዋታ ክዋኔና ፋይዳ ይዘት ተንትኖ ማሳየት ሲሆን የአጎላጎሌ&#13;
ጨዋታ ሂደቱን መተንተን፣ አጎላጎሌ የልጆች ጨዋታ ክዋኔ ላይ የሚስተዋሉ ቁሳዊ ባህሎች&#13;
(ትርጉም የሚፈልጉ ጉዳዮች) መመርመር፤ የአጎላጎሌ የልጆች ህግና የሚሰጠውን ፋይዳ&#13;
መመርመር እና በአጎላጎሌ ጨዋታ ጊዜ የልጆች ቡድን ምስረታና ሚና መጠቆምና ከክዋኔው&#13;
ጋር በተያያዘ የሚደረሱ ቃል ግጥሞችን መመርመር፤ የሚያሳዩ የምርምር ጥያቄ በማዘጋጅት&#13;
ቃለ መጠይቅ፣ምልከታ፣ተተኳሪ ቡድን ውይይት በመጠቀም መረጃዎች ተሰብስቧል፡፡ መረጃ&#13;
ሰጪዎች በዓላማ ተኮር እና በጠቋሚ ናሙና ዘዴ በመጠቀም ተመርጧል፤ መረጃዎች&#13;
በመቅረጽ ድምጽ፣ በፎቶ ካሜራና በማስታወሻ ደብተር ተሰብሰቧል፡፡ በዚህም መሠረት&#13;
የአጎላጎሌ ባህላዊ የልጆች ጨዋታ ክብረ በዓሉን ለማክበር ከሚደረጉ ቅድመ ዝግጅት እስከ&#13;
ክዋኔው መጨረሻ ድረስ ያለውን ክዋኔ ሲከውኑ የሚፈጽሙ ድርጊቶችና ቃል ግጥሞችን&#13;
ይዘት ለመመርመር በተግባራዊ ንድፍ ሃሳብ፣ በክዋኔ ተኮር ንድፍ ሃሳብና በሰነ ፍች ንድፍ&#13;
ሃሳብ ተተንትኖ ቀርቧል፡፡ የዚህ ጥናት ውጤት ማህበረሰቡ በክዋኔ አማካይነት በቀጥታም&#13;
ይሁን በተዘዋዋሪ ሃሳባቸውን በመግለጽ ሲያስተምሩበት፣ ሲመክሩበት፣ ሲዝናኑበት፣&#13;
ሃይማኖታቸውንና እምነታቸውን ሲያጸኑበት፣ የማህበረሰቡን ማንነት ሲጠብቁበት&#13;
መቆየታቸውን በትንተናው ማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህ ባህላዊ ጨዋታ አማካኝነት ልጆች&#13;
የወደፊት የሕይወታቸው መሰረት የሆነ ስርዓት የሚለምዱበት፣ ኃላፊነት መቀበልና ተግባራዊ&#13;
ማድረግን የሚማሩበት፤ የወንድነት ሚና የሚወጡበት እንደሆነ ማወቅ ተችሏል፡፡&#13;
በቤተሰቦቻቸውና በማህበረሰቡ የሚጣልባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት በአካልም ሆነ&#13;
በእዕምሮ ዝግጁ የሚሆኑበት ሃይማኖታዊ ሆነ ባህላዊ ጨዋታ መሆኑ፣ ጨዋታ የራሱ የሆነ&#13;
ህጎች ያሉትና ልጆች ከወዲሁ ህግና ደንብ ማክበርን የሚለማመዱበት፣ በጨዋታው ወቅትም&#13;
የተለያዩ ድርጊታዊ ቧልት ያላቸው ተግባራት የሚከወኑበት፣ ልጆች የሚሰባሰቡበት የራሳቸው&#13;
መስፈርት እንዳላቸው፣ በሚጫወቱበት ጊዜ የጨዋታውን ህግና ደንብ ተከትለው&#13;
እንደሚከውኑ፤ በክዋኔው በሚደረሱ የቃል ግጥሞች ይዘት ማሞካሸት፣ማሳሰብን፣ መልካም&#13;
እድል የሚገልጹ ቃል ግጥሞችን ያለው እንደሆነ ማወቅ ተችሏል፡፡ በጨዋታው አማካኝነት&#13;
እርስ በእርስ መደጋገፍን፣ መረዳዳት፣ ፍቅርን፣ አብሮ መብላትን፣ መጠጣት የሚያዳብሩበት&#13;
የትውልድ ቅብብሎሽ፣የባህል ስርጭት (መወራራስ) ያለው እንደሆነ በትንተናው ማወቅ&#13;
ተችሏል፡፡ በመሆኑም በዚህ ጨዋታ ላይ ልጆች በአካልም ሆነ በሞራልና በሰነ ልቦና ዝግጁ&#13;
እንዲሆኑና ለቀጣዩ ማህበራዊ ኑሮአቸው ልምድ የሚያዳብሩበት ጨዋታ ነው፡፡ የዚህ ጨዋታ&#13;
ጥናት በተካሄደበት ወረዳ ከሚገኙ 14 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ በተወሰኑት አካባቢዎች&#13;
ክዋኔው እየቀነሰ እንደመጣ በወረዳው ባህልና ቱሪዝም የባህል እሴት ባለሙያ የሆኑት አቶ&#13;
ሚኪያስ መለሰ 03/08/2015 ዓ/ም ጠቁሟል፡፡ በመሆኑም የአጎላጎሌ ጨዋታ ክዋኔ ቀጣይነት&#13;
እንዲኖረው የወረዳው የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ለጨዋታው አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ጥናትና&#13;
ምርምር በማድረግ ቀጣይነት እንዲኖረው ቢያደርግ፤ ጨዋታው እንዲታወቅና ጎብኝዎች&#13;
እንዲኖሩት ለማድረግም ከመገናኛ ብዙኀንና ከሚመለከታቸው ሌሎች የመንግስትና የግል&#13;
ተቋማት ጋር በጋራ ቢሰሩ፤ የመስኩ ምሁራን የበለጠ ሰፊ ጊዜና በጀት በመመደብ የጨዋታው&#13;
ክዋኔ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ በማጥናት የሚሰጠውን መጠነ ሰፊ ፋይዳ ለማህበረሰቡ&#13;
ግንዘቤ ቢሰጥ የሚል የይሁንታ ሀሳብ አለኝ፡፡
</summary>
<dc:date>2016-07-01T00:00:00Z</dc:date>
</entry>
<entry>
<title>የአብነት ተማሪዎች ማህበራዊ ህይወት በባሕር ዲር ፈሇገ ጸሏይ ቅደስ ሚካኤሌ  አንዴነት ገዲም</title>
<link href="http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15692" rel="alternate"/>
<author>
<name>እንየው, ዗ሊሇም</name>
</author>
<id>http://ir.bdu.edu.et/handle/123456789/15692</id>
<updated>2024-03-06T12:15:37Z</updated>
<published>2015-03-01T00:00:00Z</published>
<summary type="text">የአብነት ተማሪዎች ማህበራዊ ህይወት በባሕር ዲር ፈሇገ ጸሏይ ቅደስ ሚካኤሌ  አንዴነት ገዲም
እንየው, ዗ሊሇም
ይህ ጥናት የአብነት ተማሪዎች ማህበራዊ ህይወትን በባሕር ዲር ፈሇገ ጸሏይ ቅደስ ሚካኤሌ&#13;
አንዴነት ገዲም በመተንተን ተማሪዎች የሚኖራቸውን ማህበራዊ ግንኙነትና በግንኙነቱ&#13;
የሚያገኙትን ጥቅም የሚያሳይ ነው፡፡ በመሆኑም በጥናቱ ተማሪዎች የአብነት ትምህርት&#13;
ቤትን በምን አነሳሽ ምክንያት እንዯሚቀሊቀለ፤ በትምህርት ቤቱ ቆይታቸው የሚኖራቸው&#13;
ማህበራዊ ግንኙነት ምን አይነት እንዯሆነ ፤በማህበራዊ ግንኙነቶቹ የሚኖር የግሇሰብና የቡዴን&#13;
ተጠቃሚነት፤እንዱሁም በተማሪዎች መካከሌ ሇሚፈጠሩ ግጭቶች የሚፈጸሙ የግጭት&#13;
አፈታት ሂዯቶች ተተንትነዋሌ፡፡ እነዙህን መሰረታዊ የጥናቱ ዓሊማዎች ከግምት ውስጥ&#13;
በማስገባት ከመጀመሪያ የመረጃ ምንጮች በተፈጥሯዊ አውዴ ማሇትም በምሌከታ፣ በቃሇ መጠይቅና በተጠኚ ቡዴን ውይይት የተሰበሰቡ መረጃዎች በክዋኔያዊ እና በተግባራዊ ንዴፈ&#13;
ሃሳቦች መነፅርነት ተፈትሸዋሌ፡፡ የጥናት አካባቢ ሆኖ የተመረጠው ከ1955 ዓ.ም ጀምሮ&#13;
የአብነት ትምህርት የሚሰጥበት የባሕር ዲር ፈሇገ ጸሏይ ቅደስ ሚካኤሌ አንዴነት ገዲም ነው፡&#13;
፡ በመሆኑም ከአብነት ትምህርት ቤቱና ከገዲሙ 22 መረጃ አቀባዮች በዓሊማ ተኮር የናሙና&#13;
ስሌት ተመርጠው በጥናቱ ተካተዋሌ፡፡ ጥናቱ ተማሪዎች የአብነት ትምህርት ቤትን በነጻ&#13;
ፈቃዲቸው ወዯውት፤እንዱሁም በላልች አስገዲጅ ችግሮች ማሇትም ከቤተሰብና አካባቢ ምቾት&#13;
ማጣትና በአቻ ግፊት ምክንያት እንዯሚቀሊቀለ አመሊክቷሌ፡፡ በመካከሊቸው ያለ ማህበራዊ&#13;
ግንኙነቶችም በተሇያዩ ዯረጃዎች እንዯሚፈጸሙ አረጋግጧሌ፡፡ ግንኙነቶቹም ተማሪዎቹ እርስ&#13;
በርስ(የጎንዮሽ ማህበራዊ ግንኙነት)፤ከተማሪዎቹ መካከሌ በአስጠኚነትና በአሇቃነት ከሚመረጡ&#13;
ተማሪዎች ጋር(የተዋረዴ ጎንዮሽ ማህበራዊ ግንኙነት) እንዱሁም ከየኔታና ከገዲሙ&#13;
ጋር(የተዋረዴ ማህበራዊ ግንኙነት) እንዯሚፈጽሙም አመሊክቷሌ፡፡ በአብነት ትምህርት ቤቱ&#13;
በተማሪዎች መካከሌ ግጭት ቢፈጠር በአራት ዯረጃዎች ማሇትም እርስ በርስ በይቅርታ፣&#13;
በአሇቃ አሸማጋይነት፣በሰሊም ኮሚቴ ብይንና በመጨረሻም በየኔታ አማካኝነት ችግሩ ይፈታሌ፡፡&#13;
የአብነት ተማሪዎች ባሊቸው ማህበራዊ ህይወት(ግንኙነት) በመረዲዲትና በመዯጋገፍ ሊይ&#13;
የተመሰረተ ተጠቃሚነትን እንዯሚያረጋግጡም ጥናቱ አመሊክቷሌ፡፡ በመጨረሻም፤በመረጃ&#13;
ስብሰባና ትንተና ከታዩ የጥናቱ ውጤቶች በመነሳት በአብነት ተማሪዎች ጠንካራ ማህበራዊ&#13;
ግንኙነት ውስጥ ‹‹እኔ›› ሳይሆን ‹‹እኛ›› የሚሇውን ያዲበሩበትን መንገዴ ሇላሊው ማህበረሰብ&#13;
ማስተማሪያነት፤ በተሇይም መንግስት በሃገራችን የትምህርት ፖሉሲ በግብረ ገብ ትምህርት&#13;
ትግበራ ውስጥ መጠቀም ቢችሌ መሌካም ነው፡፡ በአብነት ትምህርት ቤት ውስጥ ያለ&#13;
የማህበራዊ ህይወት ግንኙነቶች በመጋራትና በመዯጋገፍ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ&#13;
ናቸው፡፡ እናም የአብነት ተማሪዎች ማህበራዊ ህይወት ውስጥ ያሇን ህብረት በማስተማሪያነት&#13;
በማ዗ጋጀት ህብረት የሚወዴ ትውሌዴ ሇመፍጠር ተግባሩ የሚመሇከተው ሁለ ሉጠቀምበት&#13;
ይገባሌ፤የአብነት ተማሪዎች በአንዴ ክፍሌ ውስጥ ከስምንት እስከ12 ኾነው እንዯመኖራቸው&#13;
አኗኗራቸው በተሇይም ሇተሊሊፊ በሽታ አጋሊጭ ሉሆን ስሇሚችሌ የተሻሇ የመኖሪያ አካባቢ&#13;
እንዱኖራቸው ገዲሙ(ቤተ ክርስቲያኗ)፣መንግስታዊም ይሁን መንግስታዊ ያሌሆኑ ተቋማት&#13;
መስራት ይገባቸዋሌ የሚለ አበይት ይሁንታዎችን በመጠቆም ጥናቱ ተቋጭቷሌ
</summary>
<dc:date>2015-03-01T00:00:00Z</dc:date>
</entry>
</feed>
